አክሱማዊነትን ያልተረዳው አክሱማዊ – (በእውቀቱ ስዩም)

አስተሳሰብህ የሰፈር
አጨዋወትህ ለማፈር
ሁኔታህ ሁሉ ባዳ ነው
አንተን ማስቀመጥ ዕዳ ነው።
                    ተመስገን ተካ 1990ዓ.ም

ሰሞኑን የጌቶቻችንን የትጥቅ ትግል ታሪክ የሚዘግቡ መፃሕፍት ታትመው እየወጡ ነው፡፡ በአብዛኛው ተመሳሳይ ናቸው። የተዋጋነው ዴሞክራሲ ለማስፈን፣ ጭቆናን ለማስወገድ፣ ብሄረሰቦችን እኩያ ለማድረግ ስንል ነው የሚል ይዘት አላቸው። ማንም አንጋፋ ታጋይ፣ ያማረኝን ለመብላት፣ ጄት የሆነ መኪና ለመንዳት፣ የእሥር ቤት ቁልፍ በእጄ ለማስገባት ስል ነው የተዋጋሁት ብሎ እንዲተርክልን አንጠብቀውም።