የክሪምያ ቀዉስና የዓለም ኤኮኖሚ

የዩክሬይን ግዛት የሆነችው ክሪምያ ባለፈው እሁድ ከሩስያ ፌዴሬሽን ጋ ዳግም ለመዋሃድ የሚያስችላትን አወዛጋቢውን ህዝበ ውሳኔ ካካሄደች በኋላ የአዉሮጳ ኅብረት አባል ሃገራት በሩስያ ላይ የመጀመርያዉን ማዕቀብ ጥለዋል። በተጣለዉ ማዕቀብ መሠረት፣ 21 ሩሲያውያን እና የክሪሚያ ባለሥልጣናት በምዕራቡ ዓለም፤