የቦምብ ጥቃትና የመቅዲሹ የፀጥታ ሁኔታ

የተመድ መቅዲሹ አዉሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ የደረሰ ፍንዳታ ህይወት አጥፍቶ ጉዳት ቢያደርስም የሶማሊያ መንግስት እንዲህ ያለ ጥቃትን ለማስቆም የሚያደርገዉን ጥረት መደገፉን እንደሚቀጥል አስታወቀ። ዋና ፀሐፊ ባን ጊሙን በጥቃቱ ህወታቸዉን ላጡት ቤተሰቦችና ለተጎዱት ሃዘናቸዉን ገልጸዋል።