22 ተኛዉ የአፍሪቃ ህብረት የመሬዎች ጉባኤ

22 ተኛው የአፍሪቃ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ተጀመረ ። ዛሬ ጠዋት የተከፈተው የዚህ ጉባኤ ይፋ አጀንዳ ግብርናና የምግብ ዋስትና የነበረ ቢሆንም በማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክና በደቡብ ሱዳን የተባባሰው ግጭት ያስከተለው ሰብዓዊ ቀውስ የጉባኤው ትኩረት በሁለቱ ሃገራት ላይ እንዲሆን አድርጓል።