“የስየ አብርሃ ሚስጥሮች” (ዘውገ ፋንታ)

የተስፋዬ ገብረአብ የመጽሐፍ-ሂሱ ሂስ

Zewge Fanta“Freedom & Justice in Ethiopia” - By Siye Abrahaዘውገ ፋንታ

መግቢያ

ደራሲው ተስፋዬ ገብረአብ፣ ስየ አብርሃ ስለጻፈው “ዝባዝንኬ” መጽሐፍ ባቀረበው “የመጽሐፍ ሂስ” ሌላ ሂስ መጻፍ ለማይቀርብ ምግብ እጅ ማስታጠብ ይሆናል። የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ተስፋዬ ገብረአብ ስለ ስየ መጽሐፍ ማሾፉን ለመቃወም ወይም ስየን ለመደገፍ አይደለም። ስየ ይህን ከጠበቀ በውጤቱ ሊበሳጭ ይችላል። ተስፋዬ ገብረአብም የስየ መጽሐፍ ውሸት የዋጠው ነው ያለውን ይህ ፀሐፊ ቢደግፍም የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ሲገለጽ የሚያረካው አይሆንም።