“የስየ አብርሃ ሚስጥሮች” (ዘውገ ፋንታ)
የተስፋዬ ገብረአብ የመጽሐፍ-ሂሱ ሂስ

ዘውገ ፋንታ
መግቢያ
ደራሲው ተስፋዬ ገብረአብ፣ ስየ አብርሃ ስለጻፈው “ዝባዝንኬ” መጽሐፍ ባቀረበው “የመጽሐፍ ሂስ” ሌላ ሂስ መጻፍ ለማይቀርብ ምግብ እጅ ማስታጠብ ይሆናል። የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ተስፋዬ ገብረአብ ስለ ስየ መጽሐፍ ማሾፉን ለመቃወም ወይም ስየን ለመደገፍ አይደለም። ስየ ይህን ከጠበቀ በውጤቱ ሊበሳጭ ይችላል። ተስፋዬ ገብረአብም የስየ መጽሐፍ ውሸት የዋጠው ነው ያለውን ይህ ፀሐፊ ቢደግፍም የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ሲገለጽ የሚያረካው አይሆንም።