የዛፎች እናት ዋንጋሪ ማታይ
የዛፎች እናት ነው ቅፅል ስማቸው- ወይዘሮ ዋንጋሪ ማታይ! በ71 ዓመታቸው በካንሰር ህመም ምክንያት ከዚህ አለም በሞት ከተለዩ ሶስት ቀናትን አስቆጠሩ። ማታይ የኖቤል የሰላም ሽልማት ያገኙ የመጀመሪያው አፍሪቃዊት ሴት ናቸው። « ልክ እንደኔ ከአዳጊ አገሮች ከተመጣ- መቼም አንድ ቀን ከመሞቴ በፊት አዳጊ የሚለውን ቃል መጠቀም አቆማለሁ ብዬ አስባለሁ!! ምክንያቱም እስከመቼ እንደምናድግ አላውቅምና! » አሉ አገራቸው ኬኒያ ከአደጉት አገራት ጎን ተሰልፋ ለማየት ሳይበቁ ማታይ ሞት ቀደማቸው። ያለፈው እሁድ በናይሮቢ ሆስቲታል ባደረባቸው የማህፀን ካንሰር ህይወታቸው አለፈች። ይሁንና ማታይ በዚች አለም እስከነበሩ ድረስ በርካታ አስተዋፅዎ ለአገራቸው ከዛም ተርፎ ለአፍሪቃ አስተዋፅዎ አድርገዋል። «ማማ ሚቲ» እያሉ ነው ኬንያውያን እኚን እውቅ ወይዘሮን ይጠሩዋቸው የነበረው። ማይታ በኬኒያ እና በሌሎች 13 የአፍሪቃ አገሮች ደኞች እንዳይጨፈጨፉ ጥረዋል። ልደት አበበ
[podcast]http://radio-download.dw.de/Events/dwelle/dira/mp3/amh/AB42DDCC_3_dwdownload.mp3[/podcast]