የአምባሣደር ዘውዴ ኃይለማርያም ሥርዓተ ቀብር በስቶክሆልም ተፈጸመ
Ethiopia Zare (ሰኞ መስከረም 15 ቀን 2004 ዓ.ም. September 26, 2011)፦ አምባሣደር ዘውዴ ኃይለማርያም በደረሰባቸው ሕመም ስቶክሆልም በሚገኘው ካሮሊንስካ ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው ቆይተው ነኀሴ ፴ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. በ፹ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ሥርዓተ ቀብራቸውም ረቡዕ መስከረም ፲ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም. ሶልና በሚገኘው በኖራ ግራቭኒንግስ ፕላትስ ተፈጽሟል።