“የብርትኳን ሳምንት” በፌስቡክ ላይ ታስቦ ሰነበተ

ከሃያ ወራት በላይ በግፍ እስር ላይ የምትገኘው የአንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ፌስቡክ በተባለው የግንኙነት መረብ ድረ-ገጽ ላይ በዚህ ሳምንት ታስባ ሰንብታለች።

ሊቀመንበሯን ለማሰብ እንቅስቃሴ የጀመሩት ኢትዮጵያውያን፣ ካለፈው ረቡእ እስከ ዛሬ መስከረም 1 ድረስ በመረቡ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ወዳጆቻቸው በሙሉ ፎቶግራፏን በየገጾቻቸው እንዲያስቀምጡ የሚጋብዝ ዘመቻ ሲያደርጉ ቆይተዋል።

ወ/ት ብርትኳን ከቅንጅት ባልደረባዎቿ ጋር ከእስር ቤት የተፈታችበትን ትክክለኛ ሁኔታ በስዊድን አገር በተደረገ ስብሰባ ላይ በማስረዳቷ እና ያንንም ቃል ለማጠፍ ፈቃደኛ ባለመሆኗ አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ በታህሳስ 2001 እንዳሰራት ይታወሳል። ከታሰረችም በኋላ በከፍተኛ ደረጃ ሰብአዊ መብቶቿ ሲጣሱ እንደቆዩ እና፤ እስካሁን ድረስ ከእናቷ እና ከአምስት አመት ልጇ በስተቀር ጠበቃዋ እና ሌሎች ወዳጅ ዘመዶች እንዲጎበኟት እንደማይፈቀድ ይታወቃል።