የተመድ እና የአፍሪቃ ህብረት ኮሚሽን ውይይት

የተመድ የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ልዑካን በአዲስ አበባ ከአፍሪቃ ህብረት ኮሚሽን ባለሥልጣናት ጋ ምክክር አካሄዱ። ባለሥልጣናቱ ከአንዱ ቀን ውይይት በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ አፍሪቃ በአህጉሯ ለሚታዩ ውዝግቦች መፍትሄ ለማሰገኘት በምታደርገው ጥረትዋ የዓለሙ መንግሥታት ድርጅት ድጋፍ እንደማይለያት ተገልጾዋል።