የHIV መድሃኒት ክትትል

UNAIDS በመድሃኒት ስርጭትና ቁጥጥር ረገድ ኢትዮጵያ ከሌሎች የአፍሪቃ ሀገሮች ጋ ስትነፃፀር በተሻለ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ የገለጸዉ በያዝነዉ ዓመት ግንቦት ወር ነዉ። እንደድርጅቱ ዘገባም በቫይረሱ አዲስ ከሚያዙት ይልቅ መድሃኒት የሚወስዱ ወገኖች ቁጥርም ከፍ ማለቱን ያመለክታል።