የሶርያ ወቅታዊ ሁኔታ

ሶሪያ ውስጥ በአምባገነኑ ገዢ በፕሬዚደንት ባሸር-አል-አሣድ ላይ የሚካሄደው ተቃውሞ በዋና ከተማይቱ በዳማስቆስ ጭምር እየጠነከረ ነው። የአገሪቱ የመብት ተቆርቋሪዎች እንዳስታወቁት ባለፈዉ አርብ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች አደባባይ ሲወጡ ከጸጥታ አስከባሪዎች ጋርም በየቦታው ግጭት ደርሶ ነበር።