አዲስ አበባ ከአፍሪካ ለኑሮ እጅግ ውድ ከተሞች መካከል ስንተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች?
በኢትዮጵያ በተለይ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ከጊዜ ወደ ጊዜ የኑሮ ውድነት እየናረ መሆኑን ነዋሪዎች ያማርራሉ። የመኖሪያ ቤት ኪራይ፣ የሸቀጦች እና የትራንስፖርት ዋጋ በከፍተኛ መጠን በከተማዋ ውድ ሆነዋል። በሌላ በኩል ከተማዋ በመሠረተ ልማት እየተሻሻለች እና እያደገች ሲሆን፣ በከተማዋ ለመኖር ዋጋው የሚቀመስ አልሆነም። ከዚህ አንጻር በኑሮ ውድነት አዲስ አበባ በአሁኑ ጊዜ ከሌሎች የአፍሪካ ከተሞች አንጻር ስንተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች?