ብላቴን ጌታ ሎሬንዞ ታዕዛዝና ኢትዮጵያዊነት
ፕ/ር ዳንኤል ክንዴ
ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ነፃነትና ዕድገት አስተዋጽኦ ያደረጉ ብዙ የኤርትራ ተወላጆች ነበሩ፣ አሁንም አሉ። ከእነዚህ ግለሰቦች መካከል ከፍተኛውን ቦታ ይዘው የሚገኙት ብላቴን ጌታ ሎሬንዞ ታዕዛዝ ናቸው። ብላቴን ጌታ ማለት የንጉሥ ዋና ጉዳይ ፈጻሚ ማለት ነው።
እኝህ ሰውዬ የት ነበር የተወለዱት? ኤርትራ የኢጣሊያን ቅኝ ግዛት በነበረችበት ወቅት እንዴት ብለው ነው ከአገራቸው ሊወጡ የቻሉት? በጊዜው ጀኔቫ በነበረው የዓለም መንግሥታት ማኅበር ውስጥ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር እንዴት ሊሆኑ ቻሉ? ከጦርነቱ በኋላስ የኢትዮጵያ የመጀመሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዴት ሊሆኑ ቻሉ? ለኢትዮጵያ ብዙ ሥራ ይሠራሉ ተብሎ ይታሰብ በነበረበት ወቅት እኝህ ታላቅ ሰው ገና በወጣትነት ዘመናቸው በተወለዱ በ46ኛው ዓመታቸው ስዊድን ላይ ሞቱ። ስለአሟሟታቸው ብዙ ነገር ይወራል፤ ዕውነቱ ግን የት ላይ ነው? … ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ