የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፎቶ ተሰረቀ
በስላቃዊ ጨዋታዎቹ የሚታወቀው ዘላለም ማልኮም ክበረት በፌስ ቡክ ግድግዳው ላይ ይህንን አስቀምጧል።
What a heartbreaking news?:
<<በአቧሬ አድዋ አደባባይ ፊት ለፊት ተሰቅሎ የነበረው እና ከ35,000 ብር በላይ የወጣበት የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ 4 ሜትር በ7 ሜትር እና ‘በዘመነ ትውልድ ያልተደፈረውን አባይ የደፈረ ጀግና’ የሚል ፅሁፍ ያለበት ግዙፍ ምስል ባልታወቁ ሰዎች ተሰረቀ>>
እንኳን የዙፋኑን ወንበር አልሰረቁት እንጅ ይሄንስ ከደመወዛችንም ቢሆን ቆርጠን ወይም ቦንድ ገዝተንም ቢሆን እንተካዋለን፡፡ ካጠፋው ልታረም አለ ሰካራም፣ አይደለም እንዴ Abe ?
የሚያሳዝነው ደግሞ የሊቀ ሊቃውንት ምስል ከተሰቀለ ገና 5 ቀን እነኳን አልሆነውም እኮ፡፡ “ጠርጥር ከገንፎ ውስጥ አለ ስንጥር” ነውና ነገሩ የሽብር ሃይላትን እጅግ ጠረጠረኩ ለአቧሬና አካባቢው ህዝብ እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ መፅናናትን እማኛለሁ፡፡
Zelalem
በርግጥ እኔ በበኩሌ ይህንን የሚያክል የጠቅላይ ሚኒስትራችን ፎቶግራፍ ገና አምስት ቀን ባልሞላ ግዜ ውስጥ መወሰዱ ጥልቅ ሀዘን ቢሆንብኝም ምናልት “ለጤንነታቸው አመቺ የሆነ ቦታ” ተወስደው ሊሆን እንደሚችልም ጠርጥሬያለሁ። አሁንም ደግሜ እመኛለሁ። ፎቶግራፋቸው ብቻ ሳይሆን እርሳቸውንም “በቂ እንክብካቤ” ወደሚያገኙበት ቦታ ብናደርሳቸው አይከፋም…!
የምር ግን ይሄ ምን ያመለክታል…?