ተመስገን ደሳለኝ 4 ወር ወይም ሁለት ሺህ ብር፤ አበበ ቀስቶ ደግሞ 8 ወር እስር ተፈረደባቸው!
የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመሰገን ደሳለኝ ከዚህ በፊት በምታወጣቸው ፅሁፎች በፍርድ ሂደቱ ላይ ጣልቃ ገብተሃል ተብሎ ተከሶ እንደነበር ይታወሳል።
ተመስገን “የተከሰሱኩት አለ አግባበብ ነው ነው” በሚል ተከራክሮ ፅሁፉ ተከሳሾች የሰጡት መሆኑን አስረድቶ ነበር። ይህንንም ለማረጋገጥ አቃቤ ህግ አበበ ቀስቶ (ክንፈሚካኤል ደበበን) ለምስክርነት ጠርቶት የነበረ ሲሆን መስካሪውም “በፅሁፉ መጠየቅ ካለብኝ የምጠየቀው እኔ ነኝ። ሃሳቤን በፍርድ ቤት ለመግለፅ ባለመቻሌ ጋዜጣ ላይ እንዲወጣ አድርጌያለሁ!” ብሎ ምስክርነቱን ሰጥቶ ነበር።
በዚህም ዛሬ ሚያዝያ 22/2004 ዓ.ም ድጋሚ ቀጠሮ ይዞ የነበረው ፍርድ ቤት በተመስገን ደሳለኝ ላይ አራት ወር እስር ወይም ሁለት ሺህ ብር እንዲሁም በአበበ ቀስቶ ላይ ወደፊት ከሚፈረድበት ላይ የሚጨመር ስምንት ወር እስራት ተፈርዶባቸዋል።
በአሁኑ ሰዓት ተመስገን በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኝ ሲሆን ከባንክ የሁለት ሺህ ብር ሲፒዮ ጓደኞቹ አሰርተው እስኪመጡለት ድረስ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል። ተመስገን ሲፒኦው ለዛሬ ካልደረሰለት ነገ የስራ ቀን ባለመሆኑ ዛሬ እና ነገን እስር ቤት ለማደር ሳይገደድ አይቀርም ሲሉ ወሬውን ያቀበሉኝ ወዳጆቼ ስጋታቸውን ገልፀውልኛል!
Filed under: Uncategorized
![]()