የሃይማኖቶ አባቶች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሀገራዊ ጥሪ ያቀርባሉ – ቅዳሜ 5 PM
በብጹህ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዮስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ የሚመራው 33ተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ህጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ ከግንቦት 1 እስከ 3 ቀን 2004 (May 9 – 11, 2012) በዋሽንግተን ዲሲ ደብረ ሃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ይካሄዳል። ቅዱስ ሲኖዶስ ወቅታዊ በሆኑ የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ መመሪያዎችን ይሰጣል፥ እንዲሁም ወቅታዊ የሀገራችን የኢትዮጵያን ሁኔታ ዳስሶና ተወያይቶ ሀገራዊ ጥሪ ለኢትዮጵያውያን ያቀርባል።
ቅዱስ ሲኖዶስ ቅዳሜ ግንቦት 4 ቀን ከ11 ሰዓት (May 12 at 5፡00 PM) በዋሽንግተን ዲሲ ደብረ ሃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
ጋዜጣዊ መግለጫውን ለማዳመጥ ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት በዚህ ስልክ ይደውሉ፣ 712 432 0075, መግቢያ ኮድ 215-557#