ሰማያዊ ፖርቲ በባህር ዳር ሊያደርገው የነበረው ህዝባዊ ስብሰባ በአገዛዙ ታገደ።

ሰማያዊ ፖርቲ በባህር ዳር ከተማ ሊያደርገው የነበረው ህዝባዊ ስብሰባ በአገዛዙ የተለመደ ኢ-ዲሞክራሲያዊ ተግባር ታገደ።
ፖርቲው በባህር ዳር ህዝባዊ ውይይት ለማድረግ ሰኔ19 ቀን2008 ዓ.ም እቅድ ይዞ የነበረ ቢሆንም ከተማ አሥተዳድሩ “በከተማ አሥተዳደሩ ሌላ ተግባራት ያለ በመሆኑ” በማለት ህዝባዊ ውይይቱ በዕለቱ እንዳይደረግ ከልክሏል።በጉዳዩ ላይ ለመወያየት የፖርቲው ሥራ አሥፈፃፊ በነገው ዕለት ሥብሰባ ያካሂዳል።