መለስ ዜናዊ 10,000 ቶን ቡና ስለመዘረፉን ያመነበት ቪዲዮ

ወያኔን ኢትዮጵያን እንደ ጠላት አገር አድርጎ ሲለሚቆጥራት ደንቆሮ ዋሻ ከነበረበት ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ደረስ ሁልቆ መሳፍርት የሌለው የአገር ሃብት እየዘረፈ እንደሚገኝ ይታወቃል። በተለይም ህወሃት የአገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ጥንካሬ ለመጠበቅ በበፊት መንግሥታት በብሔራዊ ባንክ የተቀመጠውን በብዙ ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ወርቅን ወደ ቦንዳነት መቀየሩንና 10,000 ቶን ለውጭ ገበያ የቀረበ ቡናን እንደ እንፋሎት ተኖ እንዲጠፋ ያደረገበት ምስጢር በዓለማችን በመንግሥታት ከተፈጸሙ ደረቅ ወንጀሎች የግምባር ቀደሙን ቦታ እንደሚይዙ ለመገመት አያዳግትም። 10,000 ቶን ቡና አስመልክቶ መለስ ዜናዊ እራሱ በሕዝብ ፊት ዕጁ ዝርፊያ ውስጥ መግባቱን ያመነበን ቪዲዮ ያላያችሁ እንድትመለከቱት አዚህ ላይ አቅርበንላችኋል።