የስልጤ – ቂልጦ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መቃኞ ቅዳሴ ቤት ነሐሴ 30 ይከናወናል
- ለክብረ በዓሉ እና ጽኑ ኦርቶዶክሳውያንን ለማጽናናት ምእመናን እንዲሳተፉ እየተጠየቀ ነው
- ቅዳሜ ነሐሴ 30 ቀን እና እሑድ ጳጉሜን 1 ቀን ለሚደረገው ጉዞ ምዝገባ እየተካሔደ ነው
- በክብረ በዓሉ የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ የመሠረት ድንጋይ በሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ይቀመጣል
* * *
- ከሥራቸው ታግደው በፈጠራ ክሥ የታሰሩት የሰበካ ጉባኤ አባላት ቤተሰቦች ችግር ተባብሷል
- የወረዳው ፍ/ቤት ለወሰነባቸው ከ6 – 9 ዓመት እስር ይግባኝ ለመጠየቅ ለዓርብ ቀጠሮ ተይዟል
- ከወራቤ 40 ኪ.ሜ ርቆ በሚገኘው ማረሚያ ቤት የታሰሩት አባላቱ፣ አጽናኝ ምእመናንን ይሻሉ
* * *
- ተጨማሪ 3 ምእመናት ወደ ቢሯቸው እንዳይገቡ ተከልክለዋል፤ የሥራ ልምድም ተነፍገዋል
- ነዋሪው፣ ለከት ባጣው የጠባብና የአክራሪ ባለሥልጣናት የማናለብኝነት ድርጊት ግራ ተጋብቷል
- ጠባብነት እና አክራሪነት በአመራሩ የተለያዩ ደረጃዎች እንደገነገነ ለተገለጸው ጉልሕ ማሳያ ነው

