የሕዝብ አመፅ በትያትር መድረክ

በቀድሞው የራድዮ ጣብያችን መቀመጫ በኮሎኝ ከተማ ለአስር ቀናት የአፍሪቃ ትያትር ፊልም እና ሙዚቃ ትርኢት ተካሂዶአል። ባለፈዉ ሳምንት መጠናቀቅያ ላይ ባበቃዉ በዚህ ትርኢት የአፍሪቃ ሃገራት ፖለቲካዊ ጉዳዮችን የሚያንፀባርቁ አጫጭር ቲያትሮችና የሙዚቃ ድግስ ለታዳሚዉ ቀርበዋል።