«የመጽሐፍት ማዕድ» የንባብ ባህልን ማዳበር እና ትውውቅ

በጎርጎሮሲያዊ የዘመን አቆጣጠር ወር በገባ ዘወትር በመጨረሻው ዓርብ ዕለት፤ E-within የሚባለው ድርጅት አንድ የንባብ ምሽት በአዲስ አበባ ከተማ ያዘጋጃል። «የመጽሐፍት ማዕድ» በሚል መጠሪያው የሚታወቀው ይህ ምሽት፤ ለሁሉም መጽሐፍ አፍቃሪያን ክፍት ነው።