የፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ስልጣን ዘመን መራዘም

የደቡብ ሱዳን ምክር ቤት የፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪርን የስልጣን ዘመን ለተጨማሪ ሶስት ዓመታት አራዝሟል። ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪርን እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2018 በፕሬዝዳንትነት መንበረ ስልጣኑ ላይ የሚያቆየው ውሳኔ በዋና ከተማዋ ጁባ በሚገኙ ተቃዋሚዎች ዘንድም ተቀባይነት አላገኘም። የፖለቲካ ተንታኞች ግን ጉዳዩ አዲስ አይደለም እያሉ ነው።