ለገበሬዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያቀዱት ኢትዮጵያዊ

በዓለም አቀፉ የኃይል ተቋም (International Energy Agency) መሠረት 75 በመቶ ኢትዮጵያውያን የኤሌክትሪክ ኃይል አያገኙም። ይህ የኃይል ድህነት በገጠራማ አካባቢዎች ይበረታል። አቶ ዮሴፍ ብርሃነ የኤተርኑም ኢነርጂ ቬንቸርስ (Eternum Energy Ventures )የተባለ ኩባንያ መስራች እና ባለቤት ናቸው።