የፍርድ ቤት ሰራተኞች እና የ‹ፀጥታ አካላት› የደኢህዴን አባላት መሆናቸውን ሰነዶች አረጋገጡ

ነገረ ኢትዮጵያ

በደቡብ ክልል በየም ወረዳ የሚገኙ የፍርድ ቤትና የ‹ፀጥታ› አባላት ሰራተኞች የደኢህዴን አባላት መሆናቸውን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ የላኳቸው ሰነዶች አጋለጡ፡፡ በወረዳው ፍርድ ቤቶች ከጥበቃና ፅዳት ሰራተኞች ጀምሮ እስከ አቃቤ ህጎች የደኢህዴን አባላት መሆናቸውን የ‹‹መንግስት ሰራተኛ አባላት ንኡስ ኦርኔል›› ላይ የሰፈረው የሰራተኞቹ መረጃ ያመለክታል፡፡

በተመሳሳይ በክልሉ የ‹ፀጥታ አካላትም›› የደኢህዴን አባላት እንደሆኑ መረጃው ያመለከተ ሲሆን የፀጥታ አስተዳደርና ሚሊሻዎች የድርጅት አባል መሆናቸውን ደኢህዴን የመንግስት ሰራተኞችን አባልነት የሚያስሞላበት ቅጽ ያሳያል፡፡

የፍርድ ቤት ሰራተኞቹ እና የ‹ፀጥታ አካላት›› ከ1987 ዓ.ም ጀምሮ 2005 ዓ.ም ድረስ የደኢህዴን አባል በሆኑበት ቅፅ የ‹‹ቢ እና ሲ›› የአባልነት ደረጃን እንደተሰጣቸው በሰነዱ ላይ ሰፍሯል፡፡

10425470_681524605306534_1712953591953359800_n 11063616_681524381973223_1430228779143305910_n 10924799_681524505306544_197953395506192031_n 1958113_681524511973210_7410224614414574270_n (1)
posted by Aseged Tamen

The post የፍርድ ቤት ሰራተኞች እና የ‹ፀጥታ አካላት› የደኢህዴን አባላት መሆናቸውን ሰነዶች አረጋገጡ appeared first on ሳተናው (Satenaw) -Latest Ethiopian News & Breaking News.