የደ.አፍሪቃ ጠንካራ የውጭ ዜጎች ፍልሰት መቆጣጠሪያ ሕግ

ደቡብ አፍሪቃ በሕጋዊ እና ሕገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገሯ የሚገቡ የውጭ ዜጎች ቁጥር ለመቀነስ በማሰብ ባለፈው ዓመት አንድ ጠንካራ ሕግ አውጥታለች። ከብዙ ወራት ወዲህ የተጀመረው ሕጉን ተግባራዊ የማድረጉ ሂደት ግን ብዙ ቀውስ የታየበት እና በቱሪዝም እና ከውጭ በሚገባ ወረት ላይ አሉታዊ መዘዝ አስከትሏል።