የጎሳ ፌዴራሊዝም መርዝ በኢትዮጵያ
ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)
እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የሀሰት እና የሸፍጥ የተውኔት መድረክ የተንጸባረቀበትን ህገመንግስት አርቅቆ እ.ኤ.አ ታህሳስ 8/1994 በማጽደቅ በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ጫነ። በህገ መንግስቱ ሰነድ የመጀመሪያ መግቢያ መንደርደሪያ ላይ እንዲህ የሚል ጽሁፍ ሰፍሮ ይገኛል፣ “እኛ የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች …