ላይቤሪያ እና የኢቦላ ትግል

ላይቤሪያ ከገዳዩ የኢቦላ ተህዋሲ ነጻ የምትሆንበትን ቀን በጉጉት እየጠበቀች ነው። ባለፈው ሳምንት የመጨረሻዋ የኢቦላ ህመምተኛ ከሆስፒታል ወጥተዋል።ላለፉት ሁለት ሳምንታት አዲስ የኢቦላ ህመምተኛ አለመገኘቱ ተሰምቷል።ባለፈው አመት በምዕራብ አፍሪቃ የተከሰተው የኢቦላ ተህዋሲ ወረርሽኝ ከሶስት ሺ በላይ ላይቤሪያውያንን ለሞት ዳርጓል።