ሩስያ፥ ተጠርጣሪዉ የኔምትሶቭ ገዳይ ወንጀለኛ ተባለ

የክሬምሊን ቤተ-መንግሥት ተቺ ቦሪስ ኔምትሶቭን ሩስያ መዲና ሞስኮው ክሬምሊን ቤተመንግሥት አጠገብ በጥይት ገድለዋል ተብለው በጥርጣሬ ከተያዙት ኹለት ሰዎች መካከል አንደኛው ግድያውን መፈፀሙን አምኗል መባሉ ተዘገበ። ኹለቱ በግድያ ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ከሌሎች ሦስት ተጠርጣሪዎች ጋር ሞስኮው በሚገኝ አንድ ፍርድ ቤት መቅረባቸው ተጠቅሷል።