የሞዛምቢክ መንግሥት ተቃዋሚዎች የተደቀነባቸው ስጋት

በሞዛምቢክ ታዋቂው የመንግሥቱ ተቃዋሚ ፕሮፌሰር ዢል ሲስታክ ከጥቂት ቀናት በፊት የተገደሉበት ድርጊት ሰፊ ተቃውሞ ቀሰቀሰ። የተቃውሞ ወገኖች በሕገ መንግሥታዊው የሕግ ዘርፍ ላይ ያተኮሩት ፕሮፌሰር እና ጠበቃ ሲስታክን የገደሉት የገዢው ፓርቲ፣ «ፍሬሊሞ» አክራሪ ኃይላት ተጠያቂዎች ሳይሆኑ እንዳልቀሩ ገልጸዋል። መንግሥት ይህን ወቀሳ አስተባብሏል።