የዩጋንዳ መንግሥት እና የደቡብ ሱዳን ዓማፅያን ንትርክ

ዩጋንዳ በሀገሯ የሚገኙ የደቡብ ሱዳን ዓማፅያን ሀገሯን ለቀው እንዲወጡ ከጥቂት ቀናት በፊት ትዕዛዝ አስተላልፋለች። ይኸው የዩጋንዳ ፕሬዚደንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ የወሰዱት ውሳኔ ከዓማፅያኑ ብርቱ ወቀሳ ተፈራርቆበታል።