የጋዜጠኛ ተመሥገን ደሳለኝ እናት አቤቱታ

ካለፈው ጥቅምት ወር ወዲህ በእስራት የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመሥገን ደሳለኝ እናት ወይዘሮ ፋናዬ እርዳቸው ልጃቸውን መጠየቅ እንዲችሉ በመጠየቅ ለጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት እና ለፌዴራል የሕዝብ እንባ ጠባቂ ኮሚሽን፣ እንዲሁም ለውጭ ሀገር ኤምባሲዎች ደብዳቤ መላካቸውን አስታወቁ።