የዩክሬን ዉጊያ፤ የሐያላኑ ዉዝግብና የዓለም ፀጥታ

ዲፕሎማሲዉን ደጋግሞ ከመሞከር ይልቅ ከተፋላሚ ሐይላት አንዱን ለይቶ መቅጣት፤ሌላዉን ማስታጠቁ መፍትሔ ይሆን ይሆናል።መፍትሔዉ ሠላማዊ ሊሆን ግን አይችልም።ሐያላኑ ልዩነት፤አለመግባባታቸዉን «በጠመንጃ ሐይል» ለመፍታት እያሰቡ ወይም እየሞከሩ ለደካማዉ ዓለም ችግር ፍትሐዊ መፍትሔ አለን ቢሉ ፈርቶ እንጂ ወዶና አምኖ የሚቀበል መኖሩ አጠራጣሪ ነዉ