የናይጀሪያ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ዕጩ ሙሀመድ ቡሀሪ

ባንድ ወቅት የጦር አምባገነን ነበሩ። አሁን የናይጀሪያ ፕሬዚደንት ሆነው ለመመረጥ ይፈልጋሉ። የጠቅላላ ተራማጆች ኮንግረስ ፓርቲ ዕጩ ሙሀማዱ ቡሀሪ በፕሬዚደንት ጉድላክ ጆናታን አንፃር ለፕሬዚደንታዊው ምርጫ የቀረቡ፣ ደህና ዕድል አላቸው የሚባሉ፣ በተለይ በብዛት ሙሥሊሞች የሚኖሩበት የሰሜናዊ ናይጀሪያ ሰፊ ድጋፍ ያላቸው ጠንካራ ተፎካካሪ ናቸው።