የጋውክ የታንዛኒያ ጉብኝት

የጀርመን ፕሬዝዳንት ዮአሂም ጋውክ የአምስት ቀናት የታንዛኒያ ጉብኝት ነገ ያበቃል ። የጉብኝታቸው ዋነኛ ዓላማ የረዥም ጊዜ ታሪክ ያለውን የሁለቱ አገሮች ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር ነው ። ጋውክ ከታንዛኒያ ባለሥልጣናት ጋር ከተወያዩባቸው ዐርዕስት ውስጥ የሁለቱ ሃገራት የኤኮኖሚ ግንኙነት ይገኝበታል ።