የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች በዛሬው እለት ካንጋሮ ፍርድ ቤት ቀርበዋል:: ምኒሊክ ሳልሳዊ
- ጋዜጠኛ ኤዶም ጸጉሯን በመላጨት ኢፍትሃእኢነት እና ዘረኝነት መስፋፋቱን በይፋ ተቃውማለች::
– የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ዳኛ እንዲቀየርላቸው ማመልከቻ አቅርበዋል::
በዛሬው እለት ፍርድ ቤት የቀረቡት ዞን ዘጠኝ ጦማርያን ጋዜጠኞች እንዲሁም የዲብርሃን አዘጋጅ የሆነው ዘላለም ወርቃለማሁ እና ከጋምቤላ በአሸባሪነት የተፈረጁ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል::በኢትዮጵያ የሆላንድ ኤምባሲና ሌሎች ዲፕሎማቶች በፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለመከታተል ተገኝተዋል::
በዛሬው እለት ጋዜጠኛ ኢዶም ጸጉሯን በመላጨት በወያኔ መንግስት እና በእስር ቤቱ ያለውን በፍርድ ቤቱ የሚታየውን አድልዎ የሚደርሰውን ኢፍትሃዊነት እና ዘረኝነት በመቃወም አሳይታለች::..ተከሳሽ ተብለው በወያኔ የተፈረጁት ወገኖቻችን ዳኛው እንዲቀየሩላቸው የተየቁበትን አቤቱታ ከታች ያንብቡት::

