ደላሎች ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ እንዳያከራዩ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው
‹‹ለአሸባሪ ፓርቲ ቢሮ ብታከራዩ ተጠያቂነቱን ትወስዳላችሁ›› የቂ/ክ/ከ ወረዳ 8 ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ
ነገረ ኢትዮጵያ
የቤት ደላሎች ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ እንዳያከራዩ ከቀበሌ ባለስልጣናት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ተደራጅተው በመስራት ላይ የሚገኙት ደላሎች የቂ/ክ/ከ ወረዳ 8 ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቢኒያም ከበደ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ አሸባሪ ፓርቲ ነው፡፡ ለአሸባሪ ፓርቲ ቢሮ ብታከራዩ ተጠያቂነቱን ራሳችሁ ትወስዳላችሁ›› ብለው ጥብቅ ማስጠንቀቂያ እንደሰጧቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡