የኢትዮጵያውያን ነፃነት ለማስመለስ እስከደም ጠብታ ለመክፈል የተዘጋጀ የአንድነት አባል ውርጭና ብርድ አይበግረውም!!!
ለነዚህ የኢትዮጵያ ልጆች ክብር ይገባቸዋል!!!
እነዚህ በፎቶው ላይ የምትመለከቷቸው የአንድነት ጉባኤተኞች ከመላው የኢትዮጵያ ክልሎች በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ላይ በገዢው የኢህአዲግ መንግስትና በማደጎ ልጁ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም ህሊናቸውን በገንዘብ ሽጠው አንድነትን ለመፈረካከስ ከተነሱ ጥቂት ሆድ አደር የማፊያ ቡድኖች እየተሰነዘረበት ያለውን ተከታታይና እልህ አስጨራሽ ደባ ለማክሸፍ በ24 ሰዓት ጥሪ ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው፤…… በአንድነት ፅ/ቤት በ03/05/07 ዓ.ም የሚካሄደውን ጉባኤ ለመታደም የአንድነት የክተት ጥሪ ቆራጥ ታጋዮች ናቸው፡፡ ….በፎቶዎቹ ላይ እንደምታዩት እነዚህ የኢትዮጵያን እጣ ፈንታ ለመወሰን በመታገል ላይ ያሉ ሰላማዊ ታጋዮች፤ ……ቁርጥራጭ ወረቀትና ማዳበሪያ አንጥፈው፤…… ድንኳንና ማዳበሪያ ለብሰው፤….በቀዝቃዛው የአድስ አበባ አየር የሲሚንቶ ወለል ላይ በብርድ የሚጠበሱ ቆራጥ፤ለለውጥ የተነሱና ለኢትዮጵያውያን ክብር ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው ውርጭ የሚጠጡ፤……ኢህአዲግን እንቅልፍ አሳጥተው የሚያቃዡ ጀግኖቻችን ናቸው!!! ……በእውነት ሁሉም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ክብር ሊሰጣቸው ይገባል፡፡
በኢትዮጵያውያን ህዝቦች ገንዘብ የኢህአዲግ ካድሬዎች በሊሙዚን መኪና እየተንፈላሰሱ፤……በአለም ላይ እጅግ የቅንጦት ሂወት በሚባል አኳኋን እየኖሩ፡፡ ……ውስኪና ቮድካ ጨብጠው ለቅጥረኞቻቸው በሚያስተላልፉት ቀጭን ትእዛዝ እልፍ የነፃነት አርበኞችን እያስገደሉ፤እያሳሰሩ፤እያሰደቱ…… በህዝብ ሀብት በሚንቀሳቀሰው የህዝብ ሚዲያዎች በቅንጦት ብቅ እያሉ የፍትህና ዴሞክራሲ ተረጋግጧል፤….ሀገሪቱ በሁለት ዲጂት አደገች….ምናምን እያሉ የሚደሰኩሩ አንባገነን የኢህአዲግ ባለስልጣናት ባሉበትና የኢትዮጵያውያንን ነፃነት በጠብ መንጃቸው ቁጥጥር ስር ያረጉትን ኢህአዲጋውያን፤…..ለመታገል ክብርና ነፃነታችንን ከአፈሙዛችሁ ስር ፈልቅቀን እናወጣለን ብለው በውርጭ ለሚጠበሱት የአንድነት አባላትና አመራሮች ስለእውነት የሚያስብ ሁሉ ክብርና አድናቆት ሊሰጣቸው ይገባል!!! ……ውድ የኢትዮጵያ እውነተኛ ልጆች!!! ….እመኑኝ አንድነትን ሊያቆመው የሚችል ሀይል የለም፡፡ ….የምንታገለው ምርጫን የመጨረሻ የትግል ሂደት አድርገን አይደለም፤…. በመሆኑም በነዚህ ብርቅዬ ታጋዮች ስም አንድነት ፓርቲ በተከታታይ ለሚወስናቸው ፖለቲካዊ ውሳኔዎችና የትግል ጥሪዎች አጋርነታችሁን እንድታረጋግጡ መልእክቴን አስተላልፋለሁ፡፡ ……በ2007 ኢህአዲግ የፈራው ለውጥ አይቀሬ ነው፤….ድል የህዝብ ይሆናል!!! ….ለለውጥ እንነሳ!!!








