የምርጫ ማስፈጸሚያ በጀት ክፍፍል በኢትዮጵያ

ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም ለሚካሄደው የኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርጫ እስካሁን 60 የፖለቲካ ፓርቲዎች በተሳታፊነት የምርጫ ምልክቶቻቸውን መውሰዳቸውን እና ከጥር 1 እስከ የካቲት 12 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ ባሉት 42 ቀናት ከ33 ሚሊዮን በላይ መራጮች ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።