የአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ በዛሬው ውሎ ሁለት አጀንዳዎችን አፀደቀ፡፡

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በጠራው ልዩ ጠቅላላ ጉባኤ ሁለት አጀንዳዎችን በመወያየት አፅድቋል፡፡ በመጀመሪያ አጀንዳነት የተነሳው የኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው በገዛ ፍቃዳቸው ስልጣን መልቀቃቸውን ተከትሎ ብሔራዊ ምክር ቤቱ የሰየመውን ፕሬዝደንት ተወያይቶ ያፀደቀ ሲሆን በሁለተኛ አጀንዳነት የተያዘው እና ምርጫ ቦርድ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ቁጥራችሁን አሳውቁኝ ባለው መሰረት የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ቁጥርን ወስኗል ፡፡ ጠቅላላ ጉባኤው በዛሬው ስብሰባ ከሁለቱ አጀንዳዎች በተጨማሪ በተጓደሉ የኦዲትና ኢንስፔክሽን አባላት ምክንያት የማሟያ ምርጫንም ማድረጉ ታውቋል፡፡የአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔ በነገው እለትም ቀጥሎ ይውላል፡፡udj_udj14

udj_udj13

udj_udj12

udj_udj9

udj_udj8

udj_udj7

udj_udj6

udj_udj5

udj_udj4

udj_udj3

udj_udj2

udj_udj1

10846215_387439034753787_52815730277175743_n

10420285_387439031420454_8297638254245030052_n

1526088_387439048087119_132956633100977539_n