የኬንያ ፕሬዝደንት እና «አይ ሲ ሲ»
የኬንያው ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ነው። የዛሬ ሰባት ዓመት ገደማ የኬንያ ምርጫን ተከትሎ በሃገሪቱ በተፈጠረው ፖለቲካዊ ቀውስና የብሄር ግጭት እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩት ፕሬዝደንቱ ወደ ዘሄግ ሲያቀኑ መንበረ ስልጣናቸውን በጊዜያዊነት ለምክትላቸው ዊሊያም ሩቶ ያስረክባሉ።
የኬንያው ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ነው። የዛሬ ሰባት ዓመት ገደማ የኬንያ ምርጫን ተከትሎ በሃገሪቱ በተፈጠረው ፖለቲካዊ ቀውስና የብሄር ግጭት እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩት ፕሬዝደንቱ ወደ ዘሄግ ሲያቀኑ መንበረ ስልጣናቸውን በጊዜያዊነት ለምክትላቸው ዊሊያም ሩቶ ያስረክባሉ።