የተመድ ተልዕኮ በመካከለኛዉ አፍሪቃ ሬፐብሊክ

የተመድ በመካከለኛዉ አፍሪቃ ሬፐብሊክ ዛሬ መስከረም 5 ቀን ይፋዊ ተልዕኮን ይጀምራል። በመካከለኛዉ አፍሪቃ ሬፐብሊክ ሰላም ለማምጣትና ሀገሪቱን የሚያስተዳድር መንግሥት ለመመስረት እንዲያስችል፤ የመንግሥታቱ ድርጅት ተልእኮ ለስድስት ወር ይዘልቃል መባሉ አያጠያያቂ ሆንዋል።