የሀማስ-እስራኤል ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት

እስራኤል እና ሀማስ ትናንት የደረሱት የተኩስ አቁም ስምምነት ከትናንት አስራ ሁለት ሰዓት ጀምሮ እንደፀና ይገኛል። ተቀናቃኞቹ ወገኖች በግብፅ ሸምጋይነት ነበር ሰባት ሳምንታት ለሆነው የ2,002 ሰዎች ሕይወት ላጠፋው ውጊያ ገደብ ያልተደረገበት ስምምነት የደረሱት። በስምምነቱ መሠረት፣ በጋዛ ላይ የተጣለው ዕገዳም በከፊል እንደሚነሳ ተገልጾዋል።