የዩክሬንና የሩሲያ መሪዎች ዉይይት

የምሥራቃዊ ዩክሬን አማፂያን ከሐገሪቱ መንግሥት ጦር ጋር መዋጋት ከጀመሩበት ካለፈዉ ሚያዚያ ወዲሕ ከሁለት ሺሕ በላይ ሰዎች ተገድለዋል።በአስር ሺሕ የሚቆጠሩ ተፈናቅለዋል።ጦርነቱ አማፂያኑን ትረዳለች በምትባለዉ ሩሲያና የኪየቭን መንግሥት በሚደግፉት ምዕራባዉያን መካካል ከማዕቀብ-ቅጣትና አፀፋ ቅጣት ያደረሰ ጠብ ቀስቅሷል።