18 የስደተኞች አስክሬን በላምፔዱዛ ተገኘ

የኢጣሊያ የባህር ኃይል ዛሬ እንዳስታወቀው በላምፔዱዛ የባህር መዳረሻ 18 አስክሬኖችን ሰብስቧል። የጀልባው ሞተር ላይ ጉዳት በመድረሱ ስደተኞቹ አደጋ እንደገጠማቸው ያስታወቀው የባህር ኃይል አክሎም «ሲሮ» የተባለው የባህር ኃይል መርከብ 73 ሰዎችን ከባህር ማትረፉን ገልጿል።