የመራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል የኪይቭ ጉብኝት

ዛሬ ወደ ኪይቭ የተጓዙት የጀርመንዋ መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ፔትሮ ፕሮሼንኮ ጋር ተገናኝተው ተወያዩ። ይህ በእንዲህ እንዳለ የርዳታ ቁሳቁስ የጫኑት የሩስያ ከባድ ተሽከርካሪዎች በሙሉ ከምስራቅ ዩክሬይን መዉጣታቸዉ ተነገረ።