የደቡባዊ አፍሪቃ መንግሥታት የልማት ትብብር ጉባዔ ፍፃሜ

15 ቱ የደቡባዊ አፍሪቃ መንግሥታት የልማት ትብብር ድርጅት፣ በምኅፃሩ የ«ሳዴክ» መሪዎች ያካባቢያቸውን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ለማስፋፋት ተስማሙ። የኢንዱስትሪው ዘርፍ በ«ሳዴክ» የትብብር አጀንዳ ውስጥ ዓቢይ ሚና ሊኖረው እንደሚገባ ርዕሳነ ብሔራቱ ትናንት በዚምባብዌ የሁለት ቀናት ጉባያቸውን ባጠናቀቁበት ጊዜ አስታውቀዋል።