ኢራቅ የሞት፤ሥደት፤ የጥፋት ምድር

ዲክስር ፊልክንስ በቅርቡ እንደፃፉት «ጅአፈሪን ልታስወግደዉ ትችላለሕ» ጠየቁ አሉ ቡሽ።«ምንገዶኝ» የአምባሳደሩ መልስ ነበር።ኢራቅ ሉአላዊት ሐገርናት ተብሎ የለም።ሉአላዊነቷን የሰጧት የሾሙላትን መሪ ሲያስወግዱባት ወይም የሚሹትን ሲሾሙባት ግን ሉዓላዊነቷን መዳፈር አይደለም።ጅአፈሪ ተወገዱ።ኑሪ አል-መሊኪይ ተተኩ።ባለፈዉ ሳምንት ማሊኪይ ተወገዱ።