አሳሳቢዉ የኤቦላ ተኀዋሲ ሥርጭት ምዕራብ አፍሪቃ

የኤቦላ ተኀዋሲ ወይም ቫይረስ» መዛመት እስካሁን ከታሰበዉ በላይ አስከፊ ነዉ ሲል የዓለም የጤና ድርጅት «WHO» ባለፈዉ ሳምንት ማስጠንቀቅያ ማዉጣቱ ይታወቃል። በምዕራብ አፍሪቃ በአሁኑ ወቅት በኤቦላ ቫይረስ የተያዙ አልያም በበሽታዉ የሞቱት ቁጥር በርግጥ ስንት እንደሆን መናገር አዳጋች ሆነዋል።