የኢትዮጵያና የሱዳን ወታደራዊ ኃይል ማቋቋም ስምምነት
ኢትዮጵያ እና ሱዳን የጋራ ወታደራዊ ኃይል ለመመሥረት መስማማታቸዉን በይፋ ተናግረዋል። የመገናኛ ዘዴዎች እንደዘገቡት፤ ሁለቱ ሃገራት ለማቋቋም የወሰኑት የመከላከያ ኃይል አንድ እዝ ስር የሚታዘዝ ነዉ። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ሲራጅ ፈርጌሳ፤ መሰጡት መግለጫ ጥምሩ ጦር እስከ መጭዉ መስከረም ወር ማብቂያ ድረስ እንደሚቋቋም ገልፀዋል።