የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የኢራቅ ጉብኝት

የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ዛሬ ባግዳድ ተገኝተው ለኢራቅ መንግሥት ድጋፋቸውን ገለፁ። ሀገሪቱ በአማፂ ቡድኑ ላይ የምታደርገው ትግል ትክክል መሆኑን ለኢራቁ የፖለቲካ አቻቸው ሁሴን አል ሻሪስታኒ በመግለፅ ለሀገሪቱ በአሁኑ ሰዓት ከምንም በላይ ሰብዓዊ ርዳታ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።